የሀሳብ ልዕልና ለሁለንተናዊ ብልፅግና
በክፍለ ከተማው የተጠናቀቁ እና በግንባታ ሂደት ላይ በሚገኙ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ምልከታ ተካሄደ፡፡
ኮልፌ ኮሙኒኬሽን ሐምሌ 18/2015 ዓ.ም
በተካሄደው ጉብኝት ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ፤የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው፤የክፍለ ከተማው የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ ጉልማ፤የክፍለ ከተማው ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መቆያ ላሌና የክፍለ ከተማው የዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ታደለ ቦጋለ ተገኝተዋል፡፡
በክፍለ ከተማው ወረዳ 01፤02፤03፤04፤05፤06፤07ና10 የተጠናቀቁና በግንባታ ሂደት ላይ በሚገኙ የትምህርት ቤቶች ማስፋፊያና አዲስ ግንባታዎች፣ በብሩህ ተስፋና የማነ ብርሀን ትምህርት ቤቶች የከብት እርባታ፤የዶሮ እርባታና የጓሮ አትክልት ስራዎች የተጎበኙ ሲሆን የአገልግሎት አሰጣጥጡን ለማዘመን በክፍለ ከተማው አስተዳደር እየተገነባ ያለ ኢንቲሪዬር ዲዛይን ፣የሲቪል ምዝገባና የነዋሪዎች አገልግሎት ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የነዋሪነት ጥያቄ ለመመለስ የመታወቂያ ማተሚያ ሂደቱን ለማፋጠን የተተከሉ ማሽኖች በምልከታው ተካተዋል፡፡